የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኮሌጅ የጤና ባለሙያዎች 27ኛዉን የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባኤ በበየነ መረብ ተከታተሉ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ ጥቅምት 15/2018 ዓ.ም (ቡሆዩ)

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት አመራሮችና ባለሙያዎች በጅማ ከተማ ''ዘላቂ ኢንቨስትመንት እና ኢኖቬሽን ለጠንካራ ጤና ሥርዓት '' በሚል መሪ ቃል የተካሄደውን 27ኛውን የጤና ዘርፍ ዓመታዊ ጉባዔ በበይነ መረብ በቀጥታ ተከታትሏል።

በከተማዋ የተካሄደዉ ይህ ዓመታዊ ጉባኤ ለሁለት ተከታታይ ቀናት ሲሆን የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ጤና ኢንስቲትዩት አመራሮችና የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትም ባሉበት ሆነዉ ከጥቅምት 13-14/2018 ለሁለት ቀናት በበይነ መረብ ተከታትሏል ።

Bule Hora University Has Organized Training for academic staff.

Bule Hora University, October 27, 2025 (BHU)

The academic program at Bule Hora University has organized training on the main topic, "Outcome-based curriculum revision, competency development, and academic program accreditation in line with differentiation and the university's focus areas for academic staff to create and enhance instructors' awareness.

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በተለያዩ የምርምር ሥራዎች ዙሪያ የዉስጥ ግምገማ ተካሄደ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም፣ 2018 (ቡሆዩ)

በዩኒቨርሲቲዉ የምርምር፤ስርፀትና ሥነ ምግባር ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት ከተለያዩ ኮሌጆች የተወጣጡ ምሁራን የምርምር ሥራዎቻቸዉን አቅርበዉ የዉስጥ ግምገማ ተካሂዶባቸዋል፡፡

በዕለቱ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ምርምር፤ስርፀትና ሥነ ምግባር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ዶ/ር አብነት በቀለ ሲሆኑ ለዉስጥ ግምገማ የቀረቡ የምርምር ሥራዎች በ2017 ዓ.ም በጀት ዓመት ዳይሬክቶሬቱ ጭብጥ ተኮር የምርምር ሥራዎችን ለማሰራት ያስቀመጠዉን አቅጣጫ ተከትሎ በተለያዩ ኮሌጆች ምሁራን ፕሮፖዛል ቀርበዉ፤ተገምግመዉና ተቀባይነት አገኝተዉ የተሠሩ የምርምር ሥራዎች ስለመሆናቸዉ በመግለጽ በጋራ የዉስጥ ግምገማ መደረጉ የእርስ በርስ ልምድ ልዉዉጥ እንዲደረግ ታሳቢ በማድረግ እንደ ሆነ ገልፀዋል፡፡

Pages