የመፅሀፍ ድጋፍ ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
Posted by admin on Friday, 12 November 2021የመፅሀፍ ድጋፍ ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ
የኢትዮጲያ እውቀትና ቴክኖሎጂ ሽግግር ማህበር ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመፅሀፍ ድጋፍ አደረገ።
በድጋፉ የተበረከቱት መፅሀፍት ብዛት 231/ሁለት መቶ ሰላሣ አንድ/ ሲሆኑ፤ለህክምና ትምህርት የሚጠቅሙ ናቸውም ተብሏል። የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሰቲ የጤና ኢንስቲቲዩት ዲን መ/ር ታከለ ኡቱራ የተበረከቱት መፅሀፍት በኢንስቲቲዩት የሚስተዋሉትን የመፅሀፍት እጥረት ለመቅረፍ አጋዥነታቸው ከፍተኛ ነው ብለዋል። መ/ር ታከለ ኡቱራ በሂደት ላይ ያለ የመፅሀፍ ግዥ እንዳለ አስታውሰዋል። እንደ ሜዲስንና አነስቴዥያን ያሉ ትምህርቶች የመፅሀፍት እጥረት እንደሚስተዋልባቸው ገልፀዋል።
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ "አልረሳውም እኔም የኢትዮጵያ ወታደር ነኝ "
Posted by admin on Wednesday, 3 November 2021በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ "አልረሳውም እኔም የኢትዮጵያ ወታደር ነኝ!" በሚል መሪ ቃል በሰሜን እዝ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ የተፈፀመ የግፍ ተግባር ታስቦ ዋለ።
የኢትዮጵያ የሀገር መከላከያ ሰራዊት የሀገርን ዳርድንበር ከማስከበር ባሻገር ለአለም አቀፍ፣ ለአህጉራዊና ቀጠናዊ ሠላም መረጋጋትም የደም እና የህይወት ዋጋ በመክፈል ለሠላም ዘብ የቆመ የሀገር ደጀን ነዉ።
የሀገርን ድንበር እና ሉዓላዊነት ለማስከበር ከ20 ዓመታት በላይ የሀገርን ዳር ድንበር ሌት ተቀን ሲያስከብር በቆየው የሰሜኑ ዕዝ የሀገር መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቅምት 24/2013 ዓ.ም ዘግናኝ እና ኢ-ሰብዓዊ የሆነ ጥቃት ተፈጽሟል።
የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲም ይህንን ቀን በማሰብና የሕይወት መስዋዕትነት ለከፈለውና እየከፈለ ለሚገኘው የሀገር መከላከያ ሰራዊት ደጀንነቱን ለማረጋገጥ ጥቅምት 24/2014 ዓ.ም ከማለዳው 2:30 ጀምሮ በዩኒቨርስቲው ኦዳ አዳራሽ ፊት ለፊት መርሃግብሩን አካሂዷል።
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠናቸውን 511 ተማሪዎችን አስመርቋል።
Posted by admin on Tuesday, 2 November 2021ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በመጀመሪያና በሁለተኛ ዲግሪ የሰለጠናቸውን 511 ተማሪዎችን አስመርቋል።
ከተመራቂዎቹ 363ቱ ከጤና ሳይንስ ኮሌጅ እና ከሕግ ት/ቤት በመጀመሪያ ዲግሪ በመደበኛ፣ በተከታታይ እና በክረምት ፕሮግራሞች ትምህርታቸውን የተከታተሉ ናቸው።
ቀሪዎቹ 148 ተማሪዎች በሁለተኛ ዲግሪ በመደበኛ ፕሮግራም ስልጠናቸውን እንደተከታተሉ የዩኒቨርሲቲው የኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ዳንኤል ሰይፉ ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል።
ከጠቅላላ ተመራቂዎቹ 74ቱ (22 በ2ኛ ዲግሪ) ሴት ተማሪዎች መሆናቸውን ገልጸዋል።
ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ 2 ሺህ 844 ተማሪዎችን ባለፈው ሰኔ በመጀመሪያ እና 2ኛ ዲግሪ ማስመረቁ ይታወሳል።