ጤና ኢንስቲትዩት ዕጩ ዶ/ር ዳዊት ገልገሎ እና ዕጩ ዶ/ር ሽፈራው ገልቹ የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርት (phd) የመመረቂያ የምርምር ጽሑፋቸውን አቀረቡ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 22፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
ዕጩ የሦስተኛ ዲግሪ(Phd) ተመራቂዎቹ የምርምር ሥራቸውን አዲቫይዜሮቻቸውን ጨምሮ የውጪ ገምጋሚዎችና ሌሎች ተጋባዥ ምሁራን በተገኙበት በማቅረብ በተሳካ ሁኔታ ጨርሰዋል።
በዕለቱም ዩኒቨርሲቲው በም/ፕሬዝዳንት ማዕረግ የጤና ኢንስቲትዩት ቺፍ ኤክስኪዩቲቭ ዳይሬክተር ዶ/ር ሳፋይ ኤለማ ተገኝተው ንግግር ያደረጉ ሲሆን ዕጩ የሶስተኛ ዲግሪ ተመራቂዎች ኢንስቲትዩቱ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚያስመርቃቸው በመሆኑ ለኢንስቲትዩቱም ልዩ ቀን መሆኑን የገለፁ ሲሆን ተመራቂዎቹም በወጣትነት ዕድሜያቸውና በአጭር ጊዜ ለዚህ ስኬት የበቁበት መንገድ ለሌሎች አስተማሪና የይቻላል መንፈስን ያስተማረ ነዉ ሲሉ ገልፀዋል።

Biodiversity Conversation and Ecotourism; and Wildlife Managment and Ecotoursim`` በሚል ትምህርት ፕሮግራም ዙሪያ National Level Curriculum Review ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 21፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት`` Biodiversity Conversation and Ecotourism; and Wildlife Managment and Ecotoursim`` በሚል ትምህርት ፕሮግራም ዙሪያ National Level Curriculum Review ተካሄደ።
በመንግስት ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ደረጃ የሚሰጡ ተቀራራቢ ይዘት ያላቸው የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞችን በመገምገም በስያሜ ማስተካከያ እና በተዋሄዱ ፕሮግራሞች ዙሪያ የሥርዓተ ትምህርት ክለሳ የማድረግ ሥራዎች እየተሠሩ ይገኛሉ።

Bule Hora University signed MoU with Refocus Africa Investors Network Limited.

May 16/2025: Bule Hora University
Bule Hora University (Ethiopia) and Refocus Africa Investors Network Limited (Tanzania) today announced a strategic collaboration to advance education, innovation, and sustainability across Africa. The partnership was formalized through the signing of a Memorandum of Understanding (MoU) at a ceremony held at the Inter Luxury Hotel in Addis Ababa, Ethiopia.

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የመምህራን ማህበር ሥራ አስፈፃሚዎች ምርጫ ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ ግንቦት 9፣ 2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የኢትዮጵያ መምህራን ማህበር ፕሬዝዳንት ዶ/ር ዮሐንስ በንቲ እና የኢትዮጵያ ዩኒቨርሲቲዎች መምህራን ማህበር ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ደበላሽ መንግስቱ በተገኙበት ከእያንዳንዱ ኮሌጅ ከተወከሉ መምህራን ጋር የጋራ ውይይት ተካሂዶ የማህበሩ ሥራ አስፈፃሚዎች ምርጫ ተካሂዳል።
የማህበሩ ከፍተኛ አመራሮች በዩኒቨርሲቲው የመጡበትን ዓላማ እና ማህበሩ የትምህርት ጥራትን ከማስጠበቅ አኳያም ሆነ የመምህራንን ጥቅማጥቅም ከማስጠበቅ አንፃር እያከናወነ ባለው ሥራ ዙሪያ ገለፃ አድርጓል።

Pages