በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የ2016 ዓ.ም የ4ኛ ሩብ ዓመትና የ12 ወራት ዕቅድ አፈፃፀም ሪፖርት ግምገማ እንዲሁም የ2017 በጀት ዓመት ዕቅድን በተመለከተ ዉይይት ተካሄደ፡፡
Posted by admin on Thursday, 8 August 2024ነሃሴ 01/2016 ዓ.ም
ዩኒቨርሲቲዉ በ2016 ዓ.ም ለማከናወን ያቀደዉን ዕቅድ ከመተግበር አንጻር በበጀት ዓመቱ አራተኛ ሩብ ዓመትን ጨምሮ የዓመቱ የሥራ ክንዉን በምን ደረጃ ላይ እንዳለ የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማን ጨምሮ ከፍተኛ አመራሮችና የየዘርፉ ኃላፊዎች በተገኙበት ተገምግሟል፡፡
ሪፖርቱ የቀረበዉ በዩኒቨርሲቲዉ የእስትራቴጂክ ጉዳዮች ሥራ አስፈፃሚ በአቶ መሰለ አለማየሁ ሲሆን በበጀት ዓመቱ በ4ኛ ሩብ ዓመት እና በ12 ወራት ዉስጥ የመማር ማስተማሩን ሥራ ጨምሮ ሌሎችንም ተግባራት በየግቡና በተቀመጠለት ስትራቴጅክ ዓላማ መሠረት በጠንካራ ጎን የተመዘገቡ እንዱሁም ዉስንነት የታዩባቸዉን ጉዳዮችና በትግበራ ወቅት ተግዳሮት የገጠማቸዉ እንደ ፋይናንሽያል ሪፖርት ጋር በማቀናጀት በዝርዝር አቀርበዉ ዉይይት ተደርጎባቸዋል፡፡