“ማህበራዊ ትስስራችን ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችን'' በሚል መሪ ሃሳብ በሰላም ሚኒስቴር አዘጋጅነት የውይይት ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም፣ 2018 (ቡሆዩ)

“ማህበራዊ ትስስራችን ለሕብረ-ብሔራዊ አንድነታችን'' በሚል መሪ ሃሳብ ሀገር አቀፍ የቃል-ኪዳን ቤተሰብ ማብሰሪያ የውይይት መድረክ በሰላም ሚኒስቴር አዘጋጅነት በአዳማ ከተማ ተካሂዷል።

መድረኩን በንግግር የከፈቱት የሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታና ብሔራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኒስትር ዴዔታ እና የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ከይረዲን ተዘራ (ዶ/ር) የውይይቱ መድረክ ዓላማ ጎንደር ዩኒቨርስቲ የጀመረውን የቃል ኪዳን ቤተሰብ ፕሮጀክት በሌሎች መንግስት ዩኒቨርስቲዎች እና ዩኒቨርስቲዎች የሚገኙባቸው ከተማ አስተዳዳሪዎች በመውሰድና ዕቅድ በማውጣት ወደ ሥራ የገቡትን ለማበረታታት እና በይፋ ሥራው መጀመሩን ለማብሰር መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የኦሮሚያ ስቴት ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ወደ ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ በመምጣት ከገደና ባህል ጥናት ኢንስቲትዩት ምሁራን ጋር የልምድ ልዉዉጥ አካሄዱ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም 11፣ 2018 (ቡሆዩ)

የቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የሀገር በቀል ዕዉቀትን እንድ አንድ የልህቀት ማዕከል በማድረግ የገዳና ባህል ጥናት ኢንስቲትዩት በመክፈትና ዘመናዊ ሥርዓተ ትምህርት በመቅረጽ ተማሪዎችን እስከ ሦስተኛ ዲግሪ ድረስ እያስተማረ ከመሆኑም ባሻገር የገር በቀል ዕዉቀት ለሕዝቦች ሠላምና አንድነት ያለዉን ፋይዳ የጎላ መሆኑን በመገንዘብ በቀጣይም በዘርፉ የተሻለና የተጠናከረ ሥራ ለመሥራት ዉጭ ሀገር ካሉ ዩኒቨርሲቲዎች ጋር ጭምር ትስስር በመፍጠር እየሠራ ይገኛል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ትምህርታቸዉን እየተከታተሉ ለሚገኙ የ2ኛ ዓመትና ከዚያን በላይ ለሆኑ መደበኛ ተማሪዎች የ‹‹e-SHE ( Student Success Suit ) የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም 10፣ 2018 (ቡሆዩ)

የ2018 የትምህርት ዘመን የመማር ማስተማር ሂደት ከመጀመሩ በፊት የe-SHE አስፈላጊነትና አጠቃቀምን በሚመለከት በኢ-ሌርንግ ማናጅመንት ዳይሬክቶሬት አዘጋጅነት ለመደበኛ ተማሪዎች ሥልጠና ተሰጥቷል፡፡

ሥልጠናዉን የሰጡት በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የኢ-ሌርንግ ማናጅመንት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር መ/ር ንጉስ ቢተዉ ሲሆኑ ይህ በመማር ማስተማሩ ሂደት ወሳኝ ድርሻ ያለዉ በመሆኑና በቀጣይም በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ደረጃ የበይነ መረብ የትምህርት አሰጣጥ ሂደት ተጠናክሮ የሚቀጥል በመሆኑ ተማሪዎች አስፈላጊዉን ትኩረት ሰጥተዉ እንዲከታተሉ በአንክሮ አሳስቧል፡፡

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሁለት ጆርናሎችን ለማቋቋም በቀረበዉ ጽሑፍ ላይ የዉጭ ምሁራን በተገኙበት ግምገማ ተካሄደ፡፡

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ፣ መስከረም 08፣ 2018 (ቡሆዩ)

በዩኒቨርሲቲዉ ቀደም ሲል ከነበሩት ጆርናሎች በተጨማሪ ሌሎች ሁለት ጆርናሎችን ለማቋቋም የዩኒቨርሲቲዉ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማን ጨምሮ የአካዳሚክ፤ ምርምር፤ቴክኖሎጂ ሽግግርና ማህብረሰብ አገልግሎት ም/ፕሬዝዳንት ዶ/ር ገበየሁ አሻግሬ፤የዩኒቨርሲቲዉ ምሁራንና በዘርፉ ልምድ ያካበቱ የሌሎች ዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጭምር በተገኙበት የጆርናሎቹ ረቂቅ ጽሑፍ ቀርቦ ግምገማ ተካሂዶባቸዋል፡፡

Pages