በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ለአምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ነፃ የአይን ሞራ ግርዶሽ የቀዶ ህክምና ዘመቻ ሥራ ከእቅድ በላይ በመፈፀም ተጠናቀቀ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ሐምሌ 11/2017 ዓ.ም (BHU)

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ከሐምሌ 7-11/2017 ዓ.ም ለተከታታይ አምስት ቀናት ሲካሄድ የቆየው ከክፍያ ነፃ የአይን ሞራ ግርዶሽ የቀዶ ህክምና ዘመቻ ሥራ ለ500 ግለሰቦች አግልግሎቱን ለመስጠት ታቅዶ ለ523 ሰዎች ነፃ የቀዶ ህክምና አገልግሎት በመስጠትና ከዚሁ ጋር ተያይዞ ህክምናውን ለማግኘት ወደ ሆስፒታሉ ለመጡ ነገር ግን በተደረገው ምርምራ የአይን ሞራ ግርዶሽ ጋር ያልተገናኘ ለ1200 ሰዎች ጭምር ነፃ ምርምራና አስፈላጊውን መድሃኒት በመስጠት በስኬት ስለ መጠናቀቁ ተገልፆዋል።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ``Cure Blindness``ከተባለ መንግስታዊ ካልሆነ ግብረሰናይ ድርጅት ጋር በመተባበር ነፃ የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና በዘመቻ መልክ እየተሰጠ ይገኛል።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሐምሌ 09/2017 ዓ.ም

በሀገራችን በአይን ህክምና ዙሪያ ከጤና ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ከሚሠሩት ግብረሰናይ ድርጅቶች መካከል አንዱ የሆነው ``Cure blindness project``ከቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ማስተማሪያ ሆስፒታል ጋር የመግባቢያ ስምምነት በመፍጠር ለበርካታ ዞሮች ከክፍያ ነፃ የሆነ የአይን ሞራ ግርዶሽ ቀዶ ህክምና ከመስጠቱም በላይ በርካታ የህክምና መሣሪያዎችን ጭምር ለግሷል።

በመሆኑም በተመሳሳይ መልኩ ከድርጅቱ ጋር በመተባበር ነፃ የአይን ሞራ ግርዶሽ የቀዶ ህክምና አገልግሎት ከሐምሌ 7/2017 ዓ.ም ጀምሮ ለአምስት ተከታታይ ቀናት የሚቆይ የአይን ህክምና አገልግሎት በዘመቻ መልክ በማስተማሪያ ሆስፒታሉ እየተሰጠ ይገኛል።

PhD Dissertation Defense, College of Business and Economics, Department of Economics.

June 17/2025: Bule Hora University

Mr. Defaru Adugna Faye successfully defended his PhD dissertation on June 17, 2025. The defense ceremony began with opening remarks and a welcome speech for guests by Mr. Mandho Ganale, Dean of the College of Business and Economics

Mr. Dafar's dissertation is entitled " Interplay between Capital inflow, Institutional quality and Agricultural productivity: Implications for sub-saharan Africa Economic growth, examined by a distinguished panel.

Pages