Bule Hora University and University of Piraeus Formalize Partnership with Signed Memorandum of Understanding (MoU)

Bule Hora University, Jun,4/2017:
Bule Hora University (BHU) and the University of Piraeus (UP) have officially signed a Memorandum of Understanding (MoU), marking a new partnership aimed at enhancing academic and research collaboration.
The University of Piraeus, situated in Greece, is a renowned institution dedicated to excellence in teaching and research, with a strong emphasis on economics, business, and maritime studies.

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ሕገ- ወጥ የሰዎች ዝውውርና የመንገድ ደህንነትን በሚመለከት ለተለያዩ ባለድርሻ አካላት የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠና ተሰጠ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 26፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥልጠናው በዩኒቨርሲቲው ማህብረሰብ አገልግሎት እንዲሁም በማህብረሰብ ሳይንስና ስነ ሰብ ኮሌጅ የጋራ ትብብር የተዘጋጀ ሲሆን ከምዕራብ ጉጂ ዞን እና ከቡሌ ሆራ ከተማ አስተዳደር ፣የዞንና የከተማ ፍ/ቤት ፕሬዝዳንቶች፣የዞንና የከተማ አቃበ ህግ ባለሙያዎች፣የዞንና የከተማ ትራንስፖርትና መንገድ ደህንነት ጽ/ቤት የሥራ ኃላፊዎችና ባለሙያዎች፣የዞንና የከተማ ትምህርት ጽ/ቤቶች ባለሙያዎች፣ከሴቶችና ህፃናት ጉዳይ ጽ/ቤት እና ከጉጂ ዞን የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት ተሳትፏል።

የትምህርት ሚኒስቴር ከፍተኛ ባለሙያዎች ለቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ካውንስል አባላት የአቅም ግንባታ ሥልጠና ሰጡ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 24፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በሥልጠናው ላይ የዩኒቨርሲቲው ከፍተኛ አመራሮችና በየደረጃው ያሉ የካውንስል አባላት ተሳታፊ ሆነዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ዶ/ር ብርሃኑ ለማ በሥልጠናው ቦታ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉ ሲሆን ሥልጠናው በመንግስት ደረጃ ከተሰጠን ተልዕኮና ዓላማ አንፃር በምን ደረጃ ላይ እንዳለን ራሳችንን የምንፈትሽበትና የታዩብን ውስንነቶች ካሉም በቀጣይ አሻሽለን በተሟላ ሁኔታ መፈፀም እንዲንችል አቅጣጫ የሚያሳየን ሥልጠና ነው በማለት የገለፁ ሲሆን ይህንኑ በሚመለከት ሥልጠናውን ለመስጠት በዩኒቨርሲቲው የተገኙትን የትምህርት ሚኒስቴር ባለሙያዎችን አመስግኗል።

በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ አስተባባሪነት ``AI for Academic Research`` በሚል ርዕስ ዎርክ ሾፕ ተካሄደ።

ቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ ፣ ግንቦት 22፣2017 ዓ.ም (ቡሆዩ)
በዎርክ ሾፑ ላይ ኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ከሁሉም ትምህርት ክፍሎች የተመለመሉ መምህራን የተሳተፉ ሲሆን ከተመራቂ የመጀመሪያ ዲግሪና ሁለተኛ ዲግሪ ተማሪዎች መካከልም የተወጣጡ ተማሪዎች ስለ መሳተፋቸው ተገልፆዋል።
ዎርክሾፑን የመክፈቻ ንግግር በማድረግ ያስጀመሩት የኮምፒዩቲንግና ኢንፎርማቲክስ ኮሌጅ ዲን መ/ር አሰፋ ሰንበቶ በአሁኑ ሰዓት እየኖርን ያለነው በዲጂታል ዓለም ውስጥ መሆኑንና ይህም ከጊዜ ወደ ጊዜ ከፍተኛ ለውጥ እያሳዬ መምጣቱን የጠቀሱ ሲሆን በሀገራት ኢኮኖሚ ዕድገት ዙሪያም ከፍተኛ ሚና እየተጫወተ ስለመሆኑ አስረድቷል።

Pages